Itialus A plus

Itialus A plus

Share

Outsourcing Services WallPostSoftware

10/06/2022
itialuS 03/06/2022

https://itialus.com/office/itialuS_A_plus_Quick_Service

itialuS itialuS is a global company registered in Luxembourg and has its headquartered in London-UK. itialuS Specializes in providing Financial services, Human Resource Management solutions, VAT/Tax Recovery, Compliance and Consultancy Services. itialuS is headquartered in London-UK with over 9 Offices in U...

07/05/2022

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=305022671802137&id=100068832205640

የታክስ ሕግ ተገዥነት

የታክስ ሕግ ተገዥነት ማለት መንግስታት የታክስ ገቢን ለመሰብሰብ ያወጡትን የታክስ ህጎችን፣ ደንቦችን፣ መመሪያዎችን እና መርሆዎችን በፈቃደኝነት በማክበር የግብር እና ቀረጥ ግዴታዎችን በተገቢው ጊዜ እና መንገድ መወጣት ማለት ነው፡፡ እያንዳንዱ የታክስ አስተዳዳር ከግብር ከፋዮቹ የሚጠብቀው መሠረታዊ ግዴታዎች ያሉ ሲሆን እነዚህም፡-
1. በግብር ከፋይነት መመዝገብ፣
2. ግብርን በወቅቱ እና በትክክል ማሳወቅ፣
3. በትክክል ሪፖርት ማድረግ ወይም ትክክለኛ ደጋፊ ማስረጃዎች ማቅረብ እና
4. ግብርን መክፈል ናቸው፡፡

1. በግብር ከፋይነት መመዝገብ፡- እያንዳንዱ በንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ የሚገኝ እና በግብር ከፋይነት መመዝገብ የሚጠበቅበት ግለሰብ እና ተቋም በሙሉ በራሱ ተነሳሽነት ወደ ታክስ መረቡ መምጣት እና በግብር ከፋይነት መመዝገብ ይገባዋል፡፡ መመዝገብ ለሚመለከተው የታክስ ዓይነት ሁሉ መመዝገብን ይጨምራል፡፡ ለአንዱ የታክስ ዓይነት ተመዝግቦ ለሌላው አለመመዝገብ የህግ ተገዥ አያሰኝም፡፡
በእኛ አገርም ያለው የግብር ከፋዮች ምዝገባ ሥርዓት የጣት አሻራ መስጠትን፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማውጣትን እንዲሁም እንደ አስፈላጊነቱ የሂሳብ መዝገብ መያዝን የሚያካትት በመሆኑ እያንዳንዱ ግብር ከፋይ እነዚህን ሥርዓቶች አሟልቶ በግብር ከፋይነት መመዝገብ ይጠበቅበታል፡፡
2. ታክስ ማስታወቅ፡- በሌላ በኩል ከአንድ በግብር ከፋይነት የተመዘገበ ግብር ከፋይ የሚጠበቀው ሌላኛው ግዴታ የግብር ሰብሳቢው ተቋም ባስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ እና ባስቀመጠው ግብርን የማሳወቂያ መንገድ ተጠቅሞ ለግብር ሰብሳቢው ተቋም መክፈል የሚገባውን የታክስ መጠን ማሳወቅ ነው፡፡ ይህም ማለት ከነበረው የሽያጭ መጠን እና በህግ የተፈቀዱ ተቀናሽ ወጪዎች አንጻር እንዲሁም በህግ በተቀመጡ የታክስ ቀመሮች አንጻር ለገቢ ሰብሳቢው መክፈል የሚገባው የታክስ መጠን በራሱ አስልቶ ግብር ሰብሳቢው ባስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ እና ባዘጋጀው መንገድ ማሳወቅ ነው፡፡ ገቢዎች ሚኒስቴር እንደ ታክሶቹ ዓይነት የማሳወቂያ የጊዜ ሰሌዳ ያስቀመጠ ሲሆን በተቀመጠው አግባብ ማሳወቅ ይጠበቃል፡፡

በተጨማሪም ለየታክስ/ግብር አይነቱ የተለያየ ማስታወቂያ ቅጾች የተዘጋጁ በመሆኑ ቅጾቹን በአግባቡ ሞልቶ ማቅረብ ያስፈልጋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ጀምሮም ተቋሙ ግብር ከፋዮች በኤሌክትሮኒክስ መንገድ በቀጥታ ካሉበት ሆነው ግብራቸውን የሚያሳውቁበት ስርዓርአትንም ዘርግቷል፡፡

3. ሪፖርት ማድረግ፡- የሚጠበቅበትን የግብር መጠን ያሳወቀ ግብር ከፋይ ያሳወቀው የታክስ መጠን ትክክለኛ ስለመሆኑ በደጋፊነት ሊያስረዱለት የሚችሉ የተለያዩ ሪፖርቶችን ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡ እነዚህም ሪፖርቶች በዋናነት የገቢ መግለጫ /income statement/፣ የሂሳብ መዝገብ /balance sheet/፣ የገንዘብ ፍሰት /cash flow/ እና የመሳሰሉትን ያካትታሉ፡፡

4. ታክስ መክፈል፡- በአራተኛ ደረጃ ከአንድ ግብር ከፋይ የሚጠበቀው ግዴታ በራሱ ፈቃድ መክፈል ይገባኛል በማለት አምኖ ያሳወቀውን እንዲሁም በተለያዩ ሪፖርቶች ያረጋገጠውን የታክስ መጠን በግብር ሰብሳቢው ተቋም በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት መክፈል ነው፡፡ ይህም ማለት አመታዊ የሆኑትን በየዓመቱ በተቀመጠው ጊዜ፣ ወርሃዊ እና ሌሎቹንም በተቀመጠላቸው የጊዜ ሠሌዳ መሠረት መክፈል ነው፡፡
በአጠቃላይ፤ የታክስ ህግ ተገዥነት ማለት እነዚህን እና ሌሎች ከታክስ ጋር የተገናኙ ግዴታዎችን በራስ ተነሳሽነት መወጣት ማለት ሲሆን ከገቢዎች ሚኒስቴር አንጻር የህግ ተገዥነት ማለት የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንዲያስፈጽም የተሰጡትን የጉምሩክ እና የታክስ ህጐችን፣ ደንቦችን እና መመሪያዎችን በፈቃደኝነት በማክበር፤ የግብር እና የታክስ ግዴታዎችንም መወጣት ማለት ነው፡፡

ገቢዎችን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በድረ ገጽ፦ www.mor.gov.et
በፌስቡክ፡- ministryofrevenuesofethiopia/የገቢዎች ሚኒስቴር/
በዩትዩብ፦ ministryofrevenuesofethiopia
በቴሌግራም፦ ministryofrevenuesofethiopia/የገቢዎች ሚኒስቴር/
በቴሌቪዥን ፕሮግራሞቻችን ፡- ዋልታ ቴሌቪዥን ሰኞ ማታ ከ 2፡30 ጀምሮ
ፋና ቴሌቪዥን አርብ ማታ ከ3፡00 ጀምሮ
ኢቲዮጵያ ቴሌቪዥን /ኢ.ቢ.ሲ/ ቅዳሜ ማታ ከ2፡00 ዜና በኋላ
በሬድዮ ፕሮግራሞቻችን፡- ፋና ኤፍ ኤም ሬድዮ 98.1 ሐሙስ ማታ ከ2፡30 ጀምሮ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሬድዮ 93.1 ማክሰኞ ጠዋት ከ2፡30 ጀምሮ
በወርሃዊ ጋዜጣችን፡- ገቢያችን ህልውናችን
እንዲሁም በነጻ ጥሪ አገልግሎታችን፡ - 8199 በመደወል መረጃዎችን በመጠየቅ
ስለሚከታተሉን እናመሰግናለን!

07/05/2022

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=5144730975617600&id=123960474361367

በነዳጅ ምርቶች የመሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 29፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ላለፉት አራት ወራት የዓለም አቀፍ የነዳጅ ምርቶች የመሸጫ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ተከትሎ የምርቶቹ የችርቻሮ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደረገ።

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መግለጫ፥ ከነገ ሚያዚያ 30 ጀምሮ በነዳጅ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ ማድረጉን አስታውቋል።

በታህሳስ ወር ቤንዚን በሜትሪክ ቶን 870 የአሜሪካን ዶላር እና ናፍጣ በሜትሪክ ቶን 730 የአሜሪካን ዶላር ይሸጥ ከነበረበት ሚያዚያ ወር ላይ ቤንዚን በሜትሪክ ቶን ወደ 1028 የአሜሪካ ዶላር እና ናፍጣ ደግሞ በሜትሪክ ቶን ወደ 1138 የአሜሪካን ዶላር ከፍ ማለቱን አንስቷል ሚኒስቴሩ በመግለጫው።

መንግስት የህብረተሰቡን የኑሮ ሁኔታ ታሳቢ አድርጎ ከታህሳስ 30 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለአራት ወራት ምንም አይነት ጭማሪ ሳያደርግ ቤኒዝኒን በሊትር 31 ብር ከ74 ሳንቲም፣ ናፍጣ ደግሞ በሊትር 28 ብር ከ98 ሳንቲም እንዲሸጥ ወስኖ ቆይቷልም ነው ያለው።

ይሁን እንጂ ይህ ውሳኔ በነዳጅ ማረጋጊያ ፈንድ ላይ በወር በአማካይ ወደ ተጠቃሚው መተላለፍ የነበረበት 10 ቢሊዮን ብር ጉድለት እንዲመዘገብና በመንግስት ላይም ከፍተኛ ጫና ማስከተሉን አስረድቷል።

በሚያዚያ ወር በዓለም ገበያ ነዳጅ የተገዛበት መሸጫ ዋጋን ታሳቢ በማድረግ ቀጥታ ተሰልቶ ተግባር ላይ ቢውል በአዲስ አበባ ከተማ አንድ ሊትር ናፍጣ መሸጫው 73 ብር እንደዚሁም የአንድ ሊትር ቤንዚን መሸጫ ዋጋ 66 ብር ከ78 ሳንቲም ይሆን ነበርም ብሏል።

ሆኖም ሀገሪቱ ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ ከዓለም መሸጫ ዋጋ ልዩነትን 85 በመቶ የሚሆነውን ጫና መንግስት በመሸከም ቀሪውን 15 በመቶ ለተጠቃሚው እንዲተላለፍ በመወሰን የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ መጠነኛ ክለሳ ማድረጉን ነው ያስታወቀው።

በዚህም መሰረት ከነገ ሚያዚያ 30 ጀምሮ በአዲስ አበባ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ቤንዚን በሊትር 36 ብር ከ87 ሳንቲም ፣ ነጭ ናፍጣ በሊትር 35 ብር ከ43 ሳንቲም፣ ኬሮሲን በሊትር 35 ብር ከ43 ሳንቲም፣ ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 52 ብር ከ45 ሳንቲም፣ ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 51 ብር ከ78 ሳንቲም እንዲሁም የአውሮፕላን ነዳጅ በሊትር 78 ብር ከ87 ሳንቲም እንዲሆን ተወስኗል።

ነገር ግን ይህንን መጠነኛ የነዳጅ መሸጫ ዋጋ ክለሳን ምክንያት በማድረግ በእቃዎችና አገልግሎቶች ላይ ሰው ሰራሽ እጥረት የሚፈጥሩና በምርቶች ላይ ዋጋን የሚያንሩ ህገወጥ አካላት ላይ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወስድ ያስታወቀው ሚኒስቴሩ፥ በየደረጃው ከሚገኘው የመንግስት መዋቅር ጋር በመሆን የጸጥታ አካላትና ህብረተሰቡ ተገቢውን ትብብር እንዲያደርጉ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።

27/04/2022

አብረን እንስራ

26/04/2022

itialuS Global Network is one of the largest financial and corporate services networks spanning the entire globe, composed of expert accounting, consulting, and auditing firms. Partner offices within the network are part of the outsourcing concept, and each one acts as a back-office for itialuS offices worldwide, providing a wide range of services – to the local market as well as clients across the globe.
itialuS Global provides companies across various markets and industries with cloud-based software tools to join the digital transformation initiative, where multinational businesses can expect the same consistent standards of service quality, delivery, and commitment.

Want your business to be the top-listed Accountant in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Telephone

Address


Addis Ababa