Financial Sector News of Ethiopia'' FSNE

Financial Sector News of Ethiopia'' FSNE

Share

Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Financial Sector News of Ethiopia'' FSNE, Financial Consultant, Addis Ababa.

18/06/2022

ይናገር ደሴ (ዶ/ር) የብሔራዊ ባንክ ገዥ
ብሔራዊ ባንክ የባንኮች የተቀማጭ ገንዘብ ጣሪያ ዝቅ እንዲል ወሰነ
June 15, 2022 by ኤልያስ ተገኝ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሁሉም ባንኮች ከዚህ ቀደም ከሚሰበስቡት የተጣራ ቁጠባ እንዲያስቀምጡ የሚገደዱበትን የመጠባበቂያ ገንዘብ መጠን ጣሪያ ከአሥር በመቶ ወደ ሰባት በመቶ ዝቅ እንዲል ወሰነ፡፡
ከነሐሴ 26 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ ባንኮች ከሚሰበስቡት የተጣራ ቁጠባ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እንዲያስቀምጡ የሚገደዱትን የመጠባበቂያ ገንዘብ መጠን፣ ቀድሞ ከነበረበት አምስት በመቶ ወደ አሥር በመቶ ከፍ እንዲል መወሰኑ ይታወሳል፡፡
ብሔራዊ ባንክ ከሰኔ 2 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆን ያወጣው መመርያ፣ የባንኮች የመጠባበቂያ ተቀማጭ ምጣኔ ከዚህ ቀደም ከነበረበት አሥር በመቶ ወደ ሰባት በመቶ ዝቅ እንዲል የሚያዝ ነው፡፡
በአዲሱ መመርያ መሠረት ባንኮች ከሚሰበስቡት ቁጠባ ሰባት በመቶ ያህሉን በየወሩ መጨረሻ በብሔራዊ ባንክ እንዲያስቀምጡ ይገደዳሉ፡፡
በዚህ ወቅት በተሻሻለው መመርያ የተቀማጭ ገንዘብ ጣሪያው እንዲወርድ መደረጉ፣ ምናልባትም ባንኮች እያጋጠማቸው ያለውን የጥሬ ገንዘብ እጥረት በተወሰነ ደረጃ እንዲቀረፍ ሊያግዛቸው ይችላል የሚል ዕምነት እንዳላቸው የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ፡፡
ይህም ብቻ ሳይሆን ባንኮች በተወሰነ ደረጃ ለደንበኞች ብድር ለማቅረብ ዕድል እንደሚሰጣቸው፣ ውሳኔውም በመልካምነቱ የሚወሳ መሆኑን ባለሙያዎች ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡
ብሔራዊ ባንክ ከአሥር ወራት በፊት የወሰደው የገንዘብ ፖሊሲ ዕርምጃ እየተባባሰ የመጣውን የዋጋ ንረት ለመግታት አዎንታዊ ሚና የሚጫወት፣ በኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ የጎላ አሉታዊ ተፅዕኖ የማያስከትል መሆኑን ቢገልጽም፣ በአንፃሩ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የባንክ ኃላፊዎች የመጠባበቂያ ገንዘቡ በእጥፍ መጨመሩ በባንኮች ላይ ጫና ይፈጥራል ብለው ያምናሉ፡፡
የመጠባበቂያ ገንዘብ ብሔራዊ ባንክ ያለ ምንም ወለድ የሚቀመጥ በመሆኑ ለባንኮቹ ፈታኝ እንደሆነ፣ ወለድ የሚከፍሉበት ገንዘብ ያለ ወለድ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ እንዲሆን መወሰኑ ተገቢ አለመሆኑን የባንክ ኃላፊዎች በወቅቱ ገልጸው ነበር፡፡

The Reporter

Financial Sector News of Ethiopia'' FSNE 18/06/2022

We here created this official page to provide you financial sector news ,,including
Banks news
Insurance company news
Interest free banking news
Microfinance company news
Central bank news
Issues related to capital market and any issues related to financial sector you can get from FSNE,,

Financial Sector News of Ethiopia'' FSNE Financial Consultant

Want your business to be the top-listed Accountant in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Website

Address


Addis Ababa