Samara-Logiyi Ma/Xi/Culenti k/Buxa የሠመራ - ሎግያ ከተ/መስ/ ገቢዎች ጽ/ቤት

Samara-Logiyi Ma/Xi/Culenti k/Buxa የሠመራ - ሎግያ ከተ/መስ/ ገቢዎች ጽ/ቤት

Share

Culenti Baxok Diiror Lafa!!

Photos from Samara-Logiyi Ma/Xi/Culenti k/Buxa የሠመራ - ሎግያ ከተ/መስ/ ገቢዎች ጽ/ቤት's post 21/07/2026

****ግብይት ሲፈፅሙ አገልግሎት ሲጠቀሙ ሕጋዊ ደረሰኝ በመጠየቅ የዜግነት ግዴታዎን ይወጡ****

​ለአንድ አገርና ከተማ ዘላቂ ዕድገት እንዲሁም ለተሻለ የሕዝብ አገልግሎት አቅርቦት ገቢ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። እኛ የምንከፍለው ግብርና የታክስ ክፍያ ወደ ከተማችን ልማት ተመልሶ ለትምህርት፣ ለጤና፣ ለመንገድ፣ ለንጹህ ውኃ አቅርቦት እና ለመሳሰሉት ማህበራዊ አገልግሎቶች ይውላል።
​ለከተማችን ዕድገትና ለተሻለ ነገ የበኩላችንን አወንታዊ አስተዋፅኦ ለማድረግ እነዚህን ተግባራት ያከናውኑ:
​1. የVAT ደረሰኝ መቀበልዎን ያረጋግጡ፡ ማናቸውንም ግዢዎች ሲፈጽሙ ሕጋዊ የቫት (VAT) ደረሰኝ መጠየቅ።
​2. የ5% አገልግሎት ክፍያ ደረሰኝ ይጠይቁ፡ የሆቴል ወይም የአልጋ አገልግሎት ሲጠቀሙ አዲሱን 5% የከተማ አገልግሎት ክፍያ የሚያሳይ ሕጋዊ ደረሰኝ መቆረጡን ያረጋግጡ።

- ያስታውሱ፡ ደረሰኝ መጠየቅ የከፈልነው ገንዘብ በቀጥታ ለከተማችን ልማት ገቢ መሆኑን ማረጋገጫ መንገድ ነው!
- ለአንድ ሀገርና ከተማ ገቢ ውሳኝ ነው VAT ደረሰኝ ና አዲሱን የከተማ አግልግሎት የገቢ ኮድ አልጋ ስትይዙ አግልግሎት ክፍያ 5% ደረሰኝ መቆረጡ ያረጋግጡ ለከተማ ገቢ የበኩልዎን አሰተዋጽኦ ያደረጉት
- ሕጋዊ ደረሰኝ በመጠየቅና በመቀበል ለከተማችንና ለሀገራችን ብልጽግና የበኩላችንን እንወጣ!

29/01/2026

በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የሰመራ ሎግያ ከተማ አስተዳደር ገቢ ጽ/ቤት "በከተማው የሚገኙትን ግብር ከፋዮች ባህርያት
1ኛ ለታክስ ህግ ተገዢ የሆኑ
2ኛ ለታክስ ህግ ተገዢ መሆን ፈልገው የማይሳካላቸው
3ኛ ለታክስ ህግ ተገዢ የመሆን ፍላጎት የሌላቸው በሚል በ3 ክፍሎች በመመደብ
1. ለታክስ ህግ ተገዢ የሆኑትን በማበረታታትና አገልግሎት ቅድሚያ በመስጠት፣
2. ለታክስ ህግ ተገዢ መሆን ፈልገው የማይሳካላቸውን ድጋፍ፣ስልጠና እና ምክር በመስጠት ወደ ህግ ተገዢነት እንዲመጡ ማድረግ
3. ለታክስ ህግ ተገዢ የመሆን ፍላጎት የሌላቸውን ወደ ታክስ መረቡ በማስገባት ጥብቅ ቁጥጥር እና ህጋዊ እርምጃ በመውስድ ለታክስ ህግ ተገዢ እንዲሆኑ የማድረግ ስራ በሰፊው እየሰራ እንደሆነ" የሰመራ ሎግያ ከተማ ገቢ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ Mohammed Awel ገልጸዋል።

Via Afar Mass Media Agency

13/01/2026

የሰመራ ሎግያ ከተማ ገቢዎች ፅ/ቤት ከ264 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ሰበሰበ ።

ሰመራ ፣ ጥር 5፣ 2018 (አፋ.ብ.መ.ድ)

የሰመራ ሎግያ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ፅ/ቤት በበጀት አመቱ ባለፉት 6 ወራት ከ264 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታውቋል ።

የሰመራ ሎግያ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ፅ/ቤት ሀላፊ የሆኑት አቶ መሀመድ አወል የበጀት አመት የስድስት ወራት የገቢ አሰባሰብ ሂደትን አስመልክተው ለአፋር ቴሌቪዥን መግለጫ ሰተዋል

የፅ/ቤት ሀላፊው በመግለጫቸውም በበጀት አመቱ በስድስት ወራት 284 ሚሊዮን 639 ሺህ 913 ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ከ264 ሚሊዮን 652 ሺህ ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን ተናግረው ይህም 93% ማሳካት መቻሉን ተናግረዋል

ሀላፊው አክለውም ገቢው ቀጥተኛ፤ ቀጥተኛ ካልሆኑ ታክስ እና ታክስ ካልሆኑ የገቢ አርዕስቶች የተሰበሰበ መሆኑን ጨምረው ገልፀዋል

በመጨረሻም አቶ መሀመድ አወል በቀሩት ግዜያት እቅዱን ከግብ ለማድረስ ፅ/ቤቱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆኑን በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል።

Via Afar Mass Media Agency

Want your business to be the top-listed Accountant in Logya?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Website

Address

Afar, Semera
Logya
7240