12/02/2026
"ግብር ከፋዩን በአክብሮት ማስተናገድ ይገባል"
- ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ (የገቢዎች ሚኒስትር)
የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ የ2018 የስድስት ወራት አፈጻጸም በጣም ጥሩ የሚባል መሆኑን ተናግረው ነገር ግን አሁንም የሀገራችን ታክስ ከሃገራዊ ምርት አንፃር ያለዉ ጥምርታ ከሰሃራ በታች ካሉ ሀገራት ሁሉ አነስተኛ በመሆኑ ከዚህ በላይ ጠንክሮ መስራትን ይጠይቃል አሉ፡፡
አሁን ላይ የተገኘው አፈጻጸም በራሱ አቅማችንን በመጠቀም ተጨማሪ ጥረት ብናደርግ ከዚህ በላይ መፈጸም እንደምንችል አመላካች መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ሚኒስትሯ አክለውም የታክስ አስተዳደሩ ላይ ያሉ ችሮችን ለመስተካከል በትኩረት እየተሰራ እና ውጤትም እየተገኘበት እንደሆነ ገልጸዋል። በተጨማሪም ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ግብር ከፋዩን በአክብሮት ማስተናገድ ከሁሉም እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል።
በመጨረሻም ይህንን ውጤት ማስጠበቅ ብቻ ሳይሆን ከዚህ በላይ ለመፈጸም ሁላችንም ሙሉ አቅማችንን ተጠቅመን መስራት ይጠበቅብናል ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን የ6 ወራት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በቢሾፍቱ ከተማ እየተካኼደ ነው።
(ገቢዎች)
12/02/2026